የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን እና ኦን ፕሮሞሽን ኃ/የተ/የግ/ማ (On promotion PLC) በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ለሚካሄደው አለም አቀፉ የሚዲያ ኤክስፖ በጋራ ለማዘጋጀት በዛሬው እለት የስምምነት ሰነድ ተፈራረሙ።
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ግዛው ተስፋዬ በስምምነቱ ወቅት እንደተናገሩት በአለም አቀፍ ደረጃ የሚዲያውን ዘርፍ የሚያሳድጉ ኤክስፖዎች በተለያዩ ሀገራት ይካሄዳሉ፤ በሀገራችን ደረጃም አሁን መጀመሩ ለሚዲያው እድገት ትልቅ እምርታ ነው። ስለሆነም ቀጣይነት ባለው መልኩ በትብብር እንሰራለን ብለዋል።